የአቶ በረከት ሚስት

Share

እየሩሳሌም አርዓያ በመባል የሚታወቅ ጸሃፊ ሰሞኑን በኢትዮ ሜዲያ ድረ ገጽ “ከፖለቲካ ፍጥጫው በስተጀርባ” በሚል ርእስ በጻፈው ጽሁፍ ባሁኑ ሰዓት በህውሃት እና በብአዴን መካከል እየጦፍ ያለውን የበላይነት ፉክክር በተለይም አቶ በረከት በሚመሩት እነ ወይዘሮ አዜብ መስፍንን ጄነራል ሰአረ መኮንን ቴዎድሮስ ሃጎስ ተፈራ ዋልዋ አዲሱ ለገሰን እንዲሁ ጠቅላይ ሚንስትሩን ሃይለማርያም ደሳለኝን ባቀፈው ቡድንና በተቃራኒው ደግሞ በነስብሃት ነጋ በኩል ስዩም መስፍን፣ ሃይለኪሮስ ገሰሰ፣ አባዲ ዘሞ እና ቢተው በላይን ባቀፈው ቡድን መካከል ያለውን የቡድን ፖለቲካዊ ፍጥጫ እና ሴራ አስነብበውናል:: ስለዚህ የፖለቲካ ፍጥጫ እና ሴራ መረጃ ስሌለለኝ የምለው የለኝም ::

እኔን የገረመኝ ጸሃፊው የአቶ በረከት ሚስት ወይዘሮ አሰፉ ከወይዘሮ አዜብ ጋር በሙስና መጨማለቅ መጀመሯን በጨረፍታ አንስቷል በመቀጠልም የአቶ በረከት ሚስት ወይዘሮ አሰፉ ህውሃትን አጥብቃ እንደምትጠላ እና በተደጋጋሚ ይህን አቋሟን በይፋ ስታንጸባርቅ መታየቷን ጠቅሷል:: ይህንንም ጽሁፍ ኢሳት በድረ ገጽ ዳሰሳው አቅርቦታል:: በውነቱ ጸሃፊው ያልተገነዘቡት ነገር ባሁኑ ሰዓት ህውሃትን በይፋ አጥብቆ የሚጠላ ሰው እንዴት ነው በሰላም አስመጭና ላኪ ሆኖ ንግዱን ሊያጧጡፍ የሚችለው? ለምን ይዋሻል? ጸሃፊው የአቶ ስብሃትን ቡድን በመደገፍ የአቶ በረከት ሚስት ህውሃትን ትጠላለች በማለት አዜብ መስፍንን ጄኔራል ሰዓረ መኮንን እና ቴዎድሮስ ሃጎስን ከነበረከት ቡድን እንዲርቁና ወደ አቶ ስብሃትን ቡድን እንዲቀላቀሉ ከሆነ ይንገረን በግለጽ ካለበለዚያ ግን ሁሉን አውቃለሁ ባይል ይሻለዋል:: በግሌ የአቶ በረከትን ባለቤት አውቃቸዋለሁ በፍጹም አቶ እየሩሳሌም አርዓያ እንደሚላቸው አይነት ሰው አይደሉም:: ይልቁንም ወይዘሮ አሰፉ በኢህዴን (የአሁኑ ብአዴን) ውስጥ ከናታቸው ከወንድሞቻቸው እና ከእህቶቻቸው ጋር የትግሉ መስራች በመሆን የታገሉ እና ከፍተኛ መስዋእትነት የከፈሉ ናቸው:: በትግሉም ግዜም ታጋይ እህታቸውን በጦር ሜዳ በሞት የተነጠቁ በመጨረሻ በድሉ ማግስት አብዛኛዎቹ የታገሉት እህትና ወንድሞቻቸው በህውሃት ተገፍተው ከስልጣንም ከሃብትም ባዶ እጃቸውን አጨብጭበበው የቀሩ ናቸው::

እንደሚታወቀው በዘመነ ኢሃዴግ ማናቸውም የብአዴን ሆነ የኦህዴድ ባለስልጣናት ሚስቶች ይቅርና እራሳቸው የብአዴን እና የኦህዴድ ባለስልጣናት ምንም አቅም የላቸውም:: ማንኛዋ የብአዴን ወይም የኦህዴድ ባለስልጣናት ሚስት ናት ህውሃትን በግልጽ መጥላቷ እየታወቀ ከዱባይ አዲስ አበባ ያለቀረጥ ንግዷን የምታጧጥፍ?

ባጠቃላይ የአቶ በረከትን ብአዴንን እና ኦህዴድን የአማራው እና የኦሮሞው ህዝብ ሲሰደድ ሲታሰር ሲሰደብ ሲዋረድና እና ሲገደል እያዩ አንድም ቃል ሳይተነፍሱ 20 አመት ሙሉ ህውሃትን በመፍራት ተለጣፊ በመሆናቸው ልንወቅሳቸው ይገባል:: ነገር ግን ላም ባልዋለበት ኩበት ለቀማ እንዲሉ ሊጻፍላቸው የሚገባ የሙስና እናቶች እያሉ ታግለው እንዳልታገሉ በህውሃት ተገፍተው ከስልጣንም ከሃብትም ባዶ እጃቸውን አጨብጭበበው ስለቀሩት ሳያጣሩ መዘባረቅ ያስተዛዝባል::
By: Asress M.

Share
Disclaimer: We are not responsible for any losses or damages that may have caused by using our services. EMF declines all responsibility for the contents of the materials stored by users. Each and every user is solely responsible for the posts.
Posted by on October 20, 2012. Filed under AMHARIC/አማርኛ. You can follow any responses to this entry through the RSS 2.0. You can leave a response or trackback to this entry

Leave a Reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

*



English
Amharic       Geez help: [download] [help] [keybord]

You may use these HTML tags and attributes: <a href="" title=""> <abbr title=""> <acronym title=""> <b> <blockquote cite=""> <cite> <code> <del datetime=""> <em> <i> <q cite=""> <strike> <strong>