| News sites | Audiovisuals | Advocacy groups | Political Org | Sport/culture | |
|---|---|---|---|---|---|
| » Amharic | » Abugida | » Addisdimts | » SMNE | » Andinet/UDJ | » Ethiosport |
| » Addis Voice | » Addis Neger | » DW Amharic | » EHRCO | » Andinet/USA | » ESFNA |
| » Cyberethiopia | » EcadForum | » VOA Amharic | » Advocacy Ethiopia | » EPRP | » Libro |
| » ER | » EthioGuardian | » ESAT | » Ethio American | » EPRP D | » Athletics Ethiopia |
| » Ethiofreedom | » EthiopiaZare | » Ethiotube | » NES Global | » Ginbot 7 | » AddisCulture |
| » Nazret | » Quatero | » Awrambatimes | » Gasha | » OLF | Music sites |
| » EthioMedia | Local src | » Diretube | » Amnesty | » ONLF | » Ethiosound |
| » Zehabesha | » Addisfortune | » Ethiosound | Blogs | » Timret | » Lucyzare |
| » Tadias | » Capital | » Lucyzare | » Tesfaye G/Ab | EPRDF src | » Music |
| » Africa media | » Ethiosun | » Ethiosound | » Abe Tokichaw | » Aigaforum | » » » » »» |
| » Maledatimes | » Reporter | » Ethio Diaspora | » Z'Ethiopia | » Walta | » » All Links » » |
በመስከረም 1927 ዓ.ም የወጣው Detroit Times — (Sept. 22, 1935, p. 3) መጽሔት ከአንድ ታላቅ ሳይቲስትና የፈጠራ ባለሙያ ጋር የኢትዮጵያንና የጣሊያንን ወረራ አስመልክቶ ቃለ-ምልልስ አድርጎ ነበር፡፡Nikola Tesla Tells How He’d Defend Ethiopia Against Italian Invasion(www.tesla.hu/tesla/articles/19350922.doc) በቃለ-ምልልሱም ላይ ጋዜጠኛው ዶ/ር ኒኮላ ቴስላን እንዲህ ብሎ ጠየቀው፤ “ካለፈው የካቲት 1935 (እ.አ.አ) ጀምሮ ኢጣሊያን ኢትዮጵያን በኃይል ወራለች፡፡ አንተ ንጉሠ ነገሥቱን ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ብትሆን ምን ታደርግ ነበር?” መላሹ ዶ/ር ኒኮላ ቴስላም ትንሽ ጊዜ ትክዝ ካለ በኋላ፤ “እኔ ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴን ብሆን ኖሮ፣ በከተሞች አካባቢ ያለውን ሕዝብ በመላ ወደገጠርና ወደዱር ገደሉ እንዲሄዱ አደርገዋለሁ፡፡ ሕዝቡ ከከተሞች ወጥቶ ወደገጠራማ ቦታዎች እንዲያፈገፍግ አዘዋለሁ፡፡” ጋዜጠኛው ጣልቃ ገባ፤ “ለምን?” አለው፡፡ ቴስላም ቀጠለ፤ “የአሁኗ ኢጣሊያ መሪዎች ክፉኛ ማስተዋል የጎደላቸው ጣሊያኖች ናቸው፡፡ የፋሺዝም ርዕዮት-ዓለም እውር አድርጓቸዋል፡፡ ስለሆነም ከፍተኛ ጭፍጨፋ በከተሞች በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይ እንደሚፈጽሙ ይታየኛል፡፡ ስለሆነም ሕዝቡ ከከተሞች ወጥቶ ወደ ገጠራማ አካባቢዎች ወፍለስ አለበት፡፡” ጋዜጠኛው ግራ ገባው፤ ጥያቄዎቹን አዥጎደጎደ፤ “ኢጣሊያ ትልቅ አገርና በሥልጣኔም ቢሆን ከኢትዮጵያ የተሻለች ሆና ሳለ እንዴት እንደዚህ ያለ የአረመኔዎች ግፍ ልትፈጽም ትችላለች ብለህ ታስባለህ?”