| News sites | Audiovisuals | Advocacy groups | Political Org | Sport/culture | |
|---|---|---|---|---|---|
| » Amharic | » Abugida | » Addisdimts | » SMNE | » Andinet/UDJ | » Ethiosport |
| » Addis Voice | » Addis Neger | » DW Amharic | » EHRCO | » Andinet/USA | » ESFNA |
| » Cyberethiopia | » EcadForum | » VOA Amharic | » Advocacy Ethiopia | » EPRP | » Libro |
| » ER | » EthioGuardian | » ESAT | » Ethio American | » EPRP D | » Athletics Ethiopia |
| » Ethiofreedom | » EthiopiaZare | » Ethiotube | » NES Global | » Ginbot 7 | » AddisCulture |
| » Nazret | » Quatero | » Awrambatimes | » Gasha | » OLF | Music sites |
| » EthioMedia | Local src | » Diretube | » Amnesty | » ONLF | » Ethiosound |
| » Zehabesha | » Addisfortune | » Ethiosound | Blogs | » Timret | » Lucyzare |
| » Tadias | » Capital | » Lucyzare | » Tesfaye G/Ab | EPRDF src | » Music |
| » Africa media | » Ethiosun | » Ethiosound | » Abe Tokichaw | » Aigaforum | » » » » »» |
| » Maledatimes | » Reporter | » Ethio Diaspora | » Z'Ethiopia | » Walta | » » All Links » » |
የ82 አመቱ የግብጹ መሪ ሆስኒ ሙባረክ ከ32 አመት የስልጣን ዘመን በኋላ በዛሬው እለት ስልጣን የለቀቁ ሲሆን ከነቤተሰቦቻቸው እንደጠፉ ማምሻውን ይፋ ሆኗል:: ሞባረክ ስልጣን እንዲለቁ የግብጽ ህዝብ ላለፉት 17 ቀናት የተደራጀና ያልጠቋረጠ ተቃውሞ ሲያደርግ እንደነበር ይታወሳል::
በሚሊዮን የሚቆጠር የግብጽ ህዝብ በደስታ የካይሮን ከተማ አጨናንቋታል::
የ82 አመቱ አንባገነን መሪ ስልጣን መልቀቃቸውን እና ስልጣኑን ለወታደሩ ከፍተኛ ምክር ቤት መሰጠታቸውን ምክትል ፕሬዚዳንቱ ኦማር ሱለይማን በሃገሪቱ ቴሌቭዥን አስታውቀዋል::
ሙባረክ ከመኖርያ ቤተመንግስታቸው በሁለት ሄሊኮፕተሮች የተወሰዱ ሲሆን አሁን የት እንዳሉ አይታወቅም:: በርካታ መገናኛ ብዙሃን እንደሚሉት ሙባረክ ወደ አረብ ኤሚሬት ተጉዘዋል::
የእንግሊዙ ጋርዲያን ጋዜጣ የመካከለኛው ምስራቅ ሃገሮች ምንጮችን በመጥቀስ እንደዘገበው ሙባረክ እና በተሰቡ ከ $ 40 እስከ $ 70 ቢሊዮን ዶላር እንዳካበቱ ገልጿል:: ይህ መጠን ፎርቱን መጽሄት ካወጣቸው የአለም ቁንጮ ሃብታሞች: ከሜክሲኮው ካርሎስ ስሊም ($54 ቢሊዮን) እና ከአሜሪካዊው ቢል ገትስ ($53 ቢሊዮን) ይበልጣል::
ተያይዞ በደረሰን ዜና ሙባረክ ከግብጽ ዘርፎ በስዊዝ ባንክ ያስቀመጠውን 70 ቢሊዮን ዶላር የስዊዝ መንግስት ያገደበት መሆኑን ሲ.ኤን.ኤን ዘግቧል:: ዜናው ሙባራክ በስልጣን ረጅም- እድሜ ብቻ ሳይሆን: ከአለም ሃብታሞችም በአንደኝነት ደረጃ ላይ እንደሚገኙ ይጠቁማል::
…ይህ አይነቱ ህዝባዊ ትግል እና ድል በአንባገነን ገዢዎች ስር ላሉ ህዝቦች የነጻነት ተስፋ የፈነጠቅ ሲሆን በኢትዮጵያም እንደሚቀጣጠል በስፋት እየተወራ ነው::